የሐራጅ ማስታወቂያ፤
ሕብረት ባንክ አ.ማ. በቅርንጫፎቹ በኩል ለሰጠው ብድር በመያዣነት የያዛቸውን እና ከዚህ በታች የተመለከቱትን ንብረቶች በአዋጅ ቁጥሮች 97/90 እና 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሰረት በግልፅ ሐራጅ(ጨረታ) አወዳድሮ ይሸጣል፡፡
| ተራ ቁ. | የተበዳሪ ስም | የአስያዥ ስም | አበዳሪው ቅርንጫፍ | ንብረቶቹ የሚገኙበት አድራሻና የቦታ ስፋት | የሐራጅ መነሻ ዋጋ በብር | ሐራጁ የሚካሄድበት ቀንና ሰዓት |
| 1. | ወ/ሮ ሶፋ መሃመድ የሻው | ሐሮት ፋሚሊ ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማ/ | ቦሌ ቡልቡላ | ኦሮሚያ ክልል፣ሸገር ከተማ ገላን ክ/ከተማ፣የቦታ ስፋት 5,000 ካ.ሜ የሆነ ለማኑፋክቸሪንግ አገልግሎት የሚውሉ ሁለት መጋዘኖች እና ለቢሮ አገልግሎት የሚውል G+1 ቤት | 64,916,824.00 | መጋቢት 22 ቀን /2018 ዓ.ም ዓ.ም ከጠዋቱ ከ5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት |
| 2. | አቶ ሀፍቶም ገ/ሂወት | አቶ ሀፍቶም ገ/ሂወት | አራተኛ አካባቢ ሐረር | ሐረር ከተማ፣ቀበሌ 17፣የቦታ ስፋት 250 ካ.ሜ፣ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 3,948,927.00 | መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ ከ5፡00 እስከ 6፡00 ስዓት |
| 3. | አቶ ኡመር አማን ሁሴን | አቶ ኡመር አማን ሁሴን | በሬቻ አዳማ | አዳማ ከተማ፣ቦኩሸነን ቀበሌ፣የቦታ ስፋት 180 ካ.ሜ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 5,050,688.00 | መጋቢት 23 ቀን /2018 ዓ.ም ከጧቱ ከ5:00 እስከ 6:00 ሰዓት |
| 4. | አቶ ተማም ሺፋ | አቶ ተማም ሺፋ | መናኸሪያ ጅማ | ጅማ ከተማ፣ቦሬ ቀበሌ፣የቦታ ስፋት357 ካ.ሜ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 4,284,395.00 | መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት |
| 5. | አቶ ገለታ ቁምቢ ሮባ | አቶ ዱቤ ቁምቢ ሮባ | ቡሌሆራ | ምዕራብ ጉጂ ዞን፣ቡሌሆራ ከተማ፣ቀበሌ B/Q፣የቦታ ስፋት 479.60 ካ.ሜ፣አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 3,522,780.00 | መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ ከ5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት |
| ወ/ሮ መሰረት ጳውሎስ ሙዳ | ቡሌሆራ | ምዕራብ ጉጂ ዞን፣ቡሌሆራ ከተማ፣ቀበሌ B/Q የቦታ ስፋት 320 ካ.ሜ፣አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 3,208,768.00 | መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ8፡00 እስከ 9፡00 ሰዓት | ||
| 6. | ጌቱና ዱሬሳ የሽርክና ማህበር | አቶ ዱራሳ አማን ቃሲም | አራዳ ሻሸመኔ | ሻሸመኔ ከተማ፣ደ/ቦቄ ክ/ከተማ፣ቀበሌ 04፣የቦታ ስፋት 416 ካ.ሜ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 2,000,000.00 | መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ ከ5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት |
| እነወይ/ አያንቱ አማን ቃሲም(4 ሰዎች) | አራዳ ሻሸመኔ | ሻሸመኔ ከተማ፣ደ/ቦቄ ክ/ከተማ፣ቀበሌ 04፣የቦታ ስፋት 269.22 ካ.ሜ አገልግሎቱ ለንግድ የሆነ ቤት | 2,500,000.00 | መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ8፡00 እስከ 9፡00 ሰዓት | ||
| 7. | አቶ ነስሮ ቆርሳ ደሜ | አቶ ነስሮ ቆርሳ ደሜ | ሻሸመኔ | ሻሸመኔ ከተማ፣ደ/ቦቄ ክ/ከተማ፣ቀበሌ-፣የቦታ ስፋት 62.3 ካ.ሜ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 1,519,910.00 | መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ ከ5:00 እስከ 6:00 ሰዓት |
| 8. | አቶ ሰማያት ኮይራ ኮልባዬ | አቶ ሰማያት ኮይራ ኮልባዬ | ወላይታ ሶዶ | ወላይታ ሶዶ ከተማ፣አራዳ ክ/ከተማ፣ሰላም ቀበሌ፣ የቦታ ስፋት 426.68 ካ.ሜ አገልግሎቱ ንግድ የሆነ G+5 ህንፃ | 32,104,435.00 | መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ ከ5:00 እስከ 6:00 ሰዓት |
| 9. | ወ/ሮ እየሩስ ገዳሙ አየለ | አቶ አበባው ዓለም ገድፍ | ፈለገ ህይወት | ጎጃም፣አዴት ከተማ፣ቀበሌ 05፣የቦታ ስፋት 150 ካ.ሜ፣አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 1,332,915.00 | መጋቢት 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት |
| አቶ አበባው ዓለም ገድፍ | ፈለገ ህይወት | ጎጃም፣አዴት ከተማ፣ቀበሌ 05፣የቦታ ስፋት 150 ካ.ሜ፣አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 1,278,908.00 | መጋቢት 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ8፡00 እስከ 9፡00 ሰዓት | ||
| 10. | አቶ ቻሌ ዘለቀ መንግስቱ | ወ/ሮ ዘቢደር አድማሱ ገድፍ | አዴት | ጎጃም፣አዴት ከተማ፣ቀበሌ 02፣የቦታ ስፋት 250 ካ.ሜ፣አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 648,196.00 | መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ ከ5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት |
| 11. | አቶ ባየህ እንዳለማው ገላው | አቶ ሳለአምላክ አትክልት በቀለ | ሽንዲ | ጎጃም፣ቡሬ ከተማ፣ቀበሌ 02፣የቦታ ስፋት 150 ካ.ሜ፣ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 884,075.00 | መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ8፡00 እስከ 9፡00 ሰዓት |
| አቶ እንዳለማው ገላው ሞሴ | ሽንዲ | ጎጃም፣ሽንዲ ከተማ፣ቀበሌ 01፣የቦታ ስፋት 175 ካ.ሜ፣አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 909,205.00 | መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ9፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት | ||
| 12. | አቶ ይበልጣል ድረስ አይሸሽም | አቶ ይበልጣል ድረስ አይሸሽም | አዴት በር | ጎጃም፣መራዊ፣ቀበሌ 03፣የቦታ ስፋት 200 ካ.ሜ፣ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 1,398,900.00 | መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ ከ5:00 እስከ 6:00 ሰዓት |
| ወይ/ ብርቱካን መላኩ ዋለልኝ | አዴት በር | ጎጃም፣መራዊ፣ቀበሌ 01፣የቦታ ስፋት 237.5 ካ.ሜ፣ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 1,271,188.00 | መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ8፡00 እስከ 9፡00 ሰዓት | ||
| 13. | መረባ ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማ/ | አቶ ስማቸው ጫኔ ወርቁ | ስድስት ኪሎ | ጎንደር ከተማ፣አዘዞ ክ/ከተማ፣ቀበሌ 18፣የቦታ ስፋት 150 ካ.ሜ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት፤ | 5,008,734.00 | መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት |
| ወ/ሮ አለምነሽ ደርሶ ጎቤ | ስድስት ኪሎ | ጎንደር ከተማ፣ማራኪ ክ/ከተማ፣ቀበሌ 18፣ የቦታ ስፋት 200 ካ.ሜ የሆነ መኖሪያ ቤት፤ | 6,809,132.00 | መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ8፡00 እስከ 9፡00 ሰዓት | ||
| አቶ ምስጋናው ዋኘው አበበ | ስድስት ኪሎ | ጎንደር ከተማ፣አዘዞ ክ/ከተማ፣ቀበሌ 18፣የቦታ ስፋት 150 ካ.ሜ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት፤ | 5,000,055.00 | መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ9፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት |
የሐራጅ ደንቦች፡-
- የሐራጁን መነሻ ዋጋ አንድ አራተኛ በሕብረት ባንክ አ.ማ.(Hibret Bank S.C) ስም የተሰራ የባንክ ክፍያ ማዘዣ(ሲ.ፒ.ኦ.) ብቻ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ፡፡ከባንክ ክፍያ ማዘዣ(ሲ.ፒ.ኦ) ውጭ የሚቀርብ የጨረታ ማስያዣ ተቀባይነት የለውም፡፡
- ለሐራጅ የቀረበውን ንብረት ለመጎብኘት የሚፈልግ ተጫራች ከቅርንጫፎቹ ወይም ከሕግ መምሪያ ጋር አስቀድሞ ቀጠሮ በመያዝ ከጨረታው ዕለት ሶስት ቀናት አስቀድሞ መጎብኘት ይችላል፡፡
- በሐራጅ ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች፣ተበዳሪ እና አስያዥ ብቻ ናቸው፡፡ተጫራቾች በሐራጅ ለመሳተፍ ሲመጡ መታወቂያ መያዝ ይገባቸዋል፡፡ተጫራቾች የሕግ ሰውነት የተሰጣቸው ከሆኑ ደግሞ ሕጋዊ ሰውነት ያገኙበትን የዋና ምዝገባ ምስክር ወረቀት እና ሐራጁን ለመሳተፍ የቀረበው ሰው ስልጣኑን የሚያሳይ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ወይም በተመሳሳይ አካል የፀደቀ መመስረቻ ፅሁፍ(የመተዳደሪያ ደንብ)፣ቃለ ጉባኤ ወይም የውክልና ሰነድ ይዞ መቅረብ አለበት፡፡
- ከተራ ቁጥር 1-8 የተጠቀሱት ንብረቶች ሐራጅ የሚካሄደው ንብረቶቹ በሚገኙበት ቦታ ላይ ነው፡፡ከተራ ቁጥር 9-12የተጠቀሱት ንብረቶች ሐራጅ የሚካሄደው ባህርዳር ከተማ፣ዳግማዊ ምኒልክ ክፍለ ከተማ፣ቀበሌ 14 የተባበሩት ማደያ ፊት ለፊት በሚገኘው የባንኩ ሰሜን ምዕራብ ቀጠና(ዲስትሪክት) ቢሮ ውስጥ ነው፡፡ነው፡፡በተራ ቁጥር 13 ላይ የተጠቀሰው ንብረት ጨረታ ደግሞ ጎንደር ከተማ በሚገኘው የባንኩ ፋሲል ቅርንጫፍ ውስጥ ይካሄዳል፡፡ **በተራ ቁጥር 9 ላይ የተጠቀሰው ንብረት ጨረታ ለእርማት ተብሎ በድጋሚ የወጣ ነው፡፡
- የተጫራቾች ምዝገባ ከሐራጁ መዝጊያ ሰዓት ሰላሳ ደቂቃ በፊት ይደረጋል፡፡
- ከፍ ሲል የተጠቀሱትን ንብረቶችለሚገዛና የባንኩን የብድር ፖሊሲ እና መመሪያ መመዘኛዎች ለሚያሟላ ተጫራች በሚሰጠው ከፍተኛ ዋጋ ላይ ባንኩ 50%(ሃምሳ በመቶ) ብድር ያመቻቻል፡፡
- ከፍተኛ ዋጋ ላልሰጡ ተጫራቾች ያስያዙት ገንዘብ ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል፡፡ከፍተኛ ዋጋ ለሰጠ ተጫራች ደግሞ ያቀረበውን ዋጋ ባንኩ ሲቀበለው ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ በአስራ አምስት ቀናት ውስጥ አጠቃልሎ እንዲከፍል የሚገልፅ ደብዳቤ የሚሰጠው ሲሆን በዚህ ጊዜ ውስጥ ካልከፈለ ግን ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ሐራጁ ይሰረዛል፡፡በተጨማሪም ንብረቱ በድጋሚ ለሐራጅ ሲቀርብ ለሚታየው የዋጋ ልዩነት ይጠየቃል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና ሌሎች የጨረታ አሸናፊ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰኑ ክፍያዎችን ይከፍላል፡፡
- ባንኩ ጨረታውን በማንኛውም ጊዜ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- ቦሌ ቡልቡላ ቅርንጫፍ: 0114 71 40 78/91፣ አራተኛ አካባቢ ሐረርቅርንጫፍ: 025 8 67 07 38፣ በሬቻ አዳማ ቅርንጫፍ፡ 0221-12-58-02፣ መናኸሪያ ጅማ ቅርንጫፍ 0472 11 99 42፣ ቡሌሆራ ቅርንጫፍ: 0464 43 16 48፣ አራዳ ሻሸመኔ ቅርንጫፍ: 0462 11 44 45፣ ሻሸመኔ ቅርንጫፍ፡ 046 11 10 04 36 ፣ ወላይታ ሶዶ ቅርንጫፍ፡ 046 5 51 50 16፣ ፈለገ ህይወት ቅርንጫፍ 0583 20 89 69፣ አዴት ቅርንጫፍ: 058 338 10 72 ፣ ሽንዲ ቅርንጫፍ: 058 449 07 64 ፣ አዴት በር: 058 320 31 87፣ ስድስት ኪሎ ቅርንጫፍ: 0111 22 26 06 ወይም የሕግ አገልግሎት መምሪያ: 0114 70 03 15/47 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!