የሐራጅ ማስታወቂያ፤
ሕብረት ባንክ አ.ማ. በቅርንጫፎቹ በኩል ለሰጠው ብድር በመያዣነት የያዛቸውን እና ከዚህ በታች የተመለከቱትን ንብረቶች በአዋጅ ቁጥሮች 97/90 እና 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሰረት በግልፅ ሐራጅ(ጨረታ) አወዳድሮ ይሸጣል፡፡
| ተራ ቁ. | የተበዳሪ ስም | የአስያዥ ስም | አበዳሪው ቅርንጫፍ | ቤቶቹ የሚገኙበት አድራሻና የቦታ ስፋት | የንብረቱ የይዞታ ማረጋገጫ ቁጥር | የሐራጅ መነሻ ዋጋ በብር | ሐራጁ የሚካሄድበት ቀንና ሰዓት |
| 1. | አቶ ደረጀ እንዳላማው አካሉ | ወ/ሮ ወርቅነሽ ካሳየ አየለ | ጃዊ | ጎጃም፣ጃዊ(ፈንድቃ) ከተማ፣ቀበሌ 02፣የቦታ ስፋት 220 ካ.ሜ፣ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 10186/13 | 691,034.00 | ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ ከ5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት |
| 2. | ወ/ሮ ዳሞት ደመመው አድማሱ | አቶ ገብሬ ወንድማገኝ ደስታው | ጂጋ | ጎጃም፣ጂጋ ከተማ፣ቀበሌ 02፣የቦታ ስፋት 500 ካ.ሜ፣ አገልግሎቱ ለድርጅት የሆነ ህንፃ | 9553/12 | 1,754,725.00 | ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ8፡00 እስከ 9፡00 ሰዓት |
| 3. | አቶ ታደሰ መልካም መለሰ | አቶ ታደሰ መልካም መለሰ | በረካ | መራዊ ከተማ፣ቀበሌ 01፣የቦታ ስፋት 123.29 ካ.ሜ፣ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 4963/09 | 748,660.00 | ጥር 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ ከ5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት |
| 4. | አቶ ታደሰ መልካም መለሰ | አቶ ታደሰ መልካም መለሰ | በረካ | መራዊ ከተማ፣ቀበሌ 01፣የቦታ ስፋት 69.37 ካ.ሜ፣ አገልግሎቱ ለድርጂት የሆነ ቤት | 330/13 | 667,925.00 | ጥር 27 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ8፡00 እስከ 9፡00 ሰዓት |
| 5. | አቶ ታደሰ መልካም መለሰ | አቶ ታደሰ መልካም መለሰ | በረካ | መራዊ ከተማ፣ቀበሌ- ፣የቦታ ስፋት 200 ካ.ሜ፣አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 10291/12 | 1,010,215.00 | ጥር 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ ከ5፡00 እስከ 8፡00 ሰዓት |
| 6. | አቶ ታደሰ መልካም መለሰ | አቶ አወቀ ጌታሁን | በረካ | መራዊ ከተማ፣ቀበሌ 01፣የቦታ ስፋት 173 ካ.ሜ፣አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 4827/10 | 876,452.00 | ጥር 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ8፡00 እስከ 9፡00 ሰዓት |
| 7. | አማን ሰዓዳ እና ጓደኞቻቸው ህ/ሽ/ማህበር | ወ/ሮ ፈለጉ ብዙአየሁ መኮንን | በረካ | ባህርዳር ከተማ፣ቀበሌ 04፣የቦታ ስፋት 84 ካ.ሜ አገልግሎቱ ለንግድ የሆነ ቤት | 12555/96 | 432,950.00 | ጥር 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከጠዋቱ ከ5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት |
| 8. | አቶ ይከበር አሻግሬ ውቤ | ወ/ሮ አስማረች አለሙ እንዳለው | በረካ | ባህርዳር ከተማ፣ጣና ክፍለ ከተማ፣ቀበሌ 16፣የቦታ ስፋት 250 ካ.ሜ፣አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 4052/2011 | 4,725,535.00 | ጥር 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ8፡00 እስከ 9፡00 ሰዓት |
| 9. | አቶ ዱሬሳ አማን ቃሲም እና ጌቱና ዱሬሳ የሽርክና ማህበር | አቶ ዱራሳ አማን ቃሲም | አራዳ ሻሸመኔ | ሻሸመኔ ከተማ፣ደ/ቦቄ ክ/ከተማ፣ቀበሌ 04፣የቦታ ስፋት 416 ካ.ሜ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 15738 | 2,000,000.00 | ጥር 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ ከ5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት |
| እነወይ/ አያንቱ አማን ቃሲም(4 ሰዎች) | አራዳ ሻሸመኔ | ሻሸመኔ ከተማ፣ደ/ቦቄ ክ/ከተማ፣ቀበሌ 04፣የቦታ ስፋት 269.22 ካ.ሜ አገልግሎቱ ለንግድ የሆነ ቤት | OR002040108015 | 2,500,000.00 | ጥር 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ8፡00 እስከ 9፡00 ሰዓት | ||
| 10. | አቶ በሀይሉ ተስፋዬ ወርቁ | ወ/ሮ ፀዳል ፉርጋሳ ሪፋ | ሀዋሳ | ሃዋሳ፣ታቦር ክፍለ ከተማ፣ቀበሌ ሂጣታ፣የቦታ ስፋት 200 ካ.ሜ አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ ቤት | 31796 | 5,954,597.00 | የካቲት 02 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ ከ5:00 እስከ 6:00 ሰዓት |
የሐራጅ ደንቦች፡-
- የሐራጁን መነሻ ዋጋ አንድ አራተኛ በሕብረት ባንክ አ.ማ.(Hibret Bank S.C) ስም የተሰራ የባንክ ክፍያ ማዘዣ(ሲ.ፒ.ኦ.) ብቻ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ፡፡ከባንክ ክፍያ ማዘዣ(ሲ.ፒ.ኦ) ውጭ የሚቀርብ የጨረታ ማስያዣ ተቀባይነት የለውም፡፡
- ለሐራጅ የቀረበውን ንብረት ለመጎብኘት የሚፈልግ ተጫራች ከቅርንጫፎቹ ወይም ከሕግ አገልግሎቶች መምሪያ ጋር አስቀድሞ ቀጠሮ በመያዝ ከጨረታው ዕለት ሶስት ቀናት አስቀድሞ መጎብኘት ይችላል፡፡
- በሐራጅ ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች፣ተበዳሪ እና አስያዥ ብቻ ናቸው፡፡ተጫራቾች በሐራጅ ለመሳተፍ ሲመጡ መታወቂያ መያዝ ይገባቸዋል፡፡ተጫራቾች የሕግ ሰውነት የተሰጣቸው አካላት ከሆኑ ደግሞ ሕጋዊ ሰውነት ያገኙበትን የዋና ምዝገባ ምስክር ወረቀት እና ሐራጁን ለመሳተፍ የቀረበው ሰው ስልጣኑን የሚያሳይ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ወይም በተመሳሳይ አካል የፀደቀ መመስረቻ ፅሁፍ(የመተዳደሪያ ደንብ)፣ቃለ ጉባኤ ወይም የውክልና ሰነድ ይዞ መቅረብ አለበት፡፡
- ከተራ ቁጥር 1-8 የተጠቀሱት ንብረቶች ሐራጅ የሚካሄደው ባህርዳር ከተማ፣ዳግማዊ ምኒልክ ክፍለ ከተማ፣ቀበሌ 14 የተባበሩት ማደያ ፊት ለፊት በሚገኘው የባንኩ ሰሜን ምዕራብ ቀጠና(ዲስትሪክት) ቢሮ ውስጥ ነው፡፡በተራ ቁጥር 9-10የተጠቀሱት ንብረቶች ሐራጅ የሚካሄደው ንብረቶቹ በሚገኙበት ቦታ ላይ ነው፡፡
- የተጫራቾች ምዝገባ ከሐራጁ መዝጊያ ሰዓት ሰላሳ ደቂቃ በፊት ይደረጋል፡፡
- ከፍተኛ ዋጋ ላልሰጡ ተጫራቾች ያስያዙት ገንዘብ ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል፡፡ከፍተኛ ዋጋ ለሰጠ ተጫራች ደግሞ ያቀረበውን ዋጋ ባንኩ ሲቀበለው ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ በአስራ አምስት ቀናት ውስጥ አጠቃልሎ እንዲከፍል የሚገልፅ ደብዳቤ የሚሰጠው ሲሆን በዚህ ጊዜ ውስጥ ካልከፈለ ግን ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ሐራጁ ይሰረዛል፡፡በተጨማሪም ንብረቱ በድጋሚ ለሐራጅ ሲቀርብ ለሚታየው የዋጋ ልዩነት ይጠየቃል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና ሌሎች የጨረታ አሸናፊ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰኑ ክፍያዎችን ይከፍላል፡፡
- ባንኩ ጨረታውን በማንኛውም ጊዜ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡ ጃዊቅርንጫፍ 0582 78 04 95፣ ጂጋ ቅርንጫፍ፡ 058 779 05 25፣በረካ ቅርንጫፍ፡ 0583 20 72 60፣ አራዳ ሻሸመኔ ቅርንጫፍ 0462 11 44 45፣ሀዋሳ ቅርንጫፍ፡ 0585 55 94 35፣ ወይም የሕግ አገልግሎት መምሪያ 0114 70 03 15/47 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!