የሐራጅ ማስታወቂያ፤

ሕብረት ባንክ አ.ማ. በቅርንጫፎቹ በኩል ለሰጣቸው ብድሮች በመያዣነት የያዛቸውን እና ከዚህ በታች የተመለከቱትን ንብረቶች በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሰረት በግልጽ ሐራጅ (ጨረታ) አወዳድሮ ይሸጣል፡፡ 

ተራ ቁ.የተበዳሪ ስምየአስያዥ ስምአበዳሪው ቅርንጫፍቤቶቹ የሚገኙበት አድራሻና የቦታ ስፋትየንብረቱ የይዞታ ማረጋገጫ ቁጥርየሐራጅ መነሻ ዋጋ በብርሐራጁ የሚካሄድበት ቀንና ሰዓት
1.አቶ እስክንድር ብርሃኔ ግደይወይ/ ሳራ ኪዳኔ ወ/ማርያምኢምፔርያልአዲስ አበባ ከተማ፣ቦሌ ክፍለ ከተማ፣ወረዳ 06፣የቦታ ስፋት 278 ካ/ሜ፣አገልግሎቱ ለመኖሪያ የሆነ G+2  ቤት  
 
 
ቦሌ6/2/6/7/27630/16062/02
 
 
 
50,511,632.00
የካቲት 04 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ ከ5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት
2.አቶ ተማም ሺፋአቶ ተማም ሺፋመናኸሪያ ጅማጅማ ከተማ፣ቦሬ ቀበሌ፣የቦታ ስፋት 357 ካ.ሜ፣አገልግሎቱ ለመኖሪያ  የሆነ  ቤት 
4419/2014
4,284,395.00የካቲት 04 ቀን  2018 ዓ.ም ከጠዋቱ ከ5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት
3.መኪያ እና እስማኤል የዶሮ እርባታ ሽርክና ማህበር ወይ/ መኪያ ሲራጅመናኸሪያ ጅማጅማ ከተማ፣ግንጆ ጉዱሩ ቀበሌ፣የቦታ ስፋት 200 ካ.ሜ ፣አገልግሎቱ ለመኖሪያ  የሆነ ቤት 
5430/2014
2,747,220.00የካትት 04 ቀን  2018 ዓ.ም ከቀኑ ከ8፡00 እስከ 9፡00 ሰዓት
4.ወይ/ ሀድያ አባተወይ/ ሀድያ አባተኒውላንድ ጋምቤላጋምቤላ ከተማ፣ቀቤለ 05፣የቦታ ስፋት 411 ካ.ሜ፣ አገልግሎቱ ለመኖሪያ  የሆነ ቤት  36797/15 3,391,260.00የካቲት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ከጧቱ 5፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት

የሐራጅ ደንቦች፡-

  1. የሐራጁን መነሻ ዋጋ አንድ አራተኛ በሕብረት ባንክ አ.ማ.(Hibret Bank  S.C) ስም የተሰራ የባንክ ክፍያ ማዘዣ(ሲ.ፒ.ኦ.) ብቻ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ፡፡ከባንክ ክፍያ ማዘዣ(ሲ.ፒ.ኦ) ውጭ የሚቀርብ የጨረታ ማስያዣ ተቀባይነት የለውም፡፡
  2. ለሐራጅ የቀረበውን ንብረት ለመጎብኘት የሚፈልግ ተጫራች ከቅርንጫፎቹ ወይም ከሕግ አገልግሎቶች መምሪያ ጋር አስቀድሞ ቀጠሮ በመያዝ ከጨረታው ዕለት ሶስት ቀናት አስቀድሞ መጎብኘት ይችላል፡፡ 
  3. በሐራጅ ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች፣ተበዳሪ እና አስያዥ ብቻ ናቸው፡፡ተጫራቾች በሐራጅ ለመሳተፍ ሲመጡ መታወቂያ መያዝ ይገባቸዋል፡፡ተጫራቾች የሕግ ሰውነት የተሰጣቸው አካላት ከሆኑ ደግሞ ሕጋዊ ሰውነት ያገኙበትን የዋና ምዝገባ ምስክር ወረቀት እና ሐራጁን ለመሳተፍ የቀረበው ሰው ስልጣኑን የሚያሳይ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ፅ/ቤት ወይም በተመሳሳይ አካል የፀደቀ መመስረቻ ፅሁፍ(የመተዳደሪያ ደንብ)፣ቃለ ጉባኤ ወይም የውክልና ሰነድ ይዞ መቅረብ አለበት፡፡
  4. በተራ ቁጥር 1 ላይ የተመለከተውን ንብረት ብቻ ለሚገዛና የባንኩን የብድር ፖሊሲ እና መመሪያ መመዘኛዎች ለሚያሟላ ተጫራች በሚሰጠው ከፍተኛ ዋጋ ላይ ባንኩ 50%(ሃምሳ በመቶ) ብድር ሊያመቻች ይችላል፡፡
  5. በተራ ቁጥር 1 ላይ የተጠቀሰው ንብረት ሐራጅ የሚካሄደው የሕብረት ባንክ አ.ማ ዋና መስሪያ ቤት ሕንፃ (ሕብር ታወር) 26ኛ ፎቅ የሕግ አገልግሎት መምሪያ ባለው የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ ነው፡፡ የሌሎች ንብረቶች ሐራጅ የሚካሄደው ንብረቶቹ በሚገኙበት ቦታ ላይ ነው፡፡
  6. የተጫራቾች ምዝገባ ከሐራጁ መዝጊያ ሰዓት ሰላሳ ደቂቃ በፊት ይደረጋል፡፡
  7. ከፍተኛ ዋጋ ላልሰጡ ተጫራቾች ያስያዙት ገንዘብ ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል፡፡ከፍተኛ ዋጋ ለሰጠ ተጫራች ደግሞ ያቀረበውን ዋጋ ባንኩ ሲቀበለው ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ በአስራ አምስት ቀናት ውስጥ አጠቃልሎ እንዲከፍል የሚገልፅ ደብዳቤ የሚሰጠው ሲሆን በዚህ ጊዜ ውስጥ ካልከፈለ ግን ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ሐራጁ ይሰረዛል፡፡በተጨማሪም ንብረቱ በድጋሚ ለሐራጅ ሲቀርብ ለሚታየው የዋጋ ልዩነት ይጠየቃል፡፡
  8. የጨረታው አሸናፊ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና ሌሎች የጨረታ አሸናፊ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰኑ ክፍያዎችን ይከፍላል፡፡
  9. ባንኩ ጨረታውን በማናቸውም ጊዜ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡ ኢምፔርያል ቅርንጫፍ 0116 60 94 16፣ መናኸሪያ ጅማ ቅርንጫፍ፡ 0472 11 99 42፣ ኒውላንድ ጋምቤላ ቅርንጫፍ፡ 0475 51 27 02 ወይም የሕግ አገልግሎት መምሪያ፡  0114 70 03 15/47 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!

Similar Posts