የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር ሕባ009/2018
ሕብረት ባንክ አ.ማ ለሰጠው ብድር በዋስትናነት የተረከባቸውን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ንብረቶች (የባንክ አክሲዮኖች) ባሉበት ሁኔታ በዝግ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
| ተ.ቁ | የንብረቱ ዓይነት | የባለቤትነት መታወቂያ ቁጥር/ የሼር ቁጥር | የአክሲዮኑ ባለቤት /Certificate Issuer | የጨረታ መነሻ ዋጋ በብር |
| 1 | የባንክ አክሲዮኖች/ሼር | AAG7188፣ AAI07188 | አንበሳ ባንክ አ.ማ | 2,914,850.05 |
| 2 | የባንክ አክሲዮኖች/ሼር | 6962 | ወጋገን ባንክ አ.ማ | 764,000.00 |
| 3 | የባንክ አክሲዮኖች/ሼር | 6955፣9412፣ 08167፣ 10714፣ 12733፣ 13158፣ 14204፣ 15179 | ወጋገን ባንክ አ.ማ | 1,200,000.00 |
| 4 | የባንክ አክሲዮኖች/ሼር | 09927 | ብርሃን ባንክ | 207,000.00 |
| 5 | የባንክ አክሲዮኖች/ሼር | 19277፣ 19037 | አንበሳ ባንክ አ.ማ | 2,422,198.80 |
| 6 | የባንክ አክሲዮኖች/ሼር | 007456 | አንበሳ ባንክ አ.ማ | 411,774.00 |
በመሆኑም
- ተጫራቾች የጨረታውን መነሻ ዋጋ አንድ አራተኛ (1/4) በሕብረት ባንክ አ.ማ (Hibret Bank S.C) ስም የተሰራ የባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲ.ፒ.ኦ) ብቻ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ::
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ 15% ተ.እ.ታን የሚያካትት ወይም የማያካትት ስለመሆኑ በግልጽ ማስፈር ይኖርባቸዋል፣ ነገር ግን ይህ ሳይገለጽ ቢቀር ተጫራቾች በሚያቀርቡት የመወዳደሪያ ዋጋ ላይ ባንኩ ተጨማሪ 15% ተ.እ.ታን በመደምር የሚያወዳድር ይሆናል፡፡
- ከፍተኛ ዋጋ ላልሰጡ ተጫራቾች ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ ወዲያዉኑ ይመለስላቸዋል፡፡ አሸናፊ የሆነው ተጫራች ደግሞ ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ በአስር ቀናት ውስጥ አጠቃልሎ ካልከፈለ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ጨረታው ይሰረዛል፡፡
- ተጫራቾች ንብረቶቹን/አክሲዮኖቹን የሚገዙበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ በባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ንብረት አስተዳደር ዋና ክፍል ሕብር ታወር 4ኛ ፎቅ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጥር 07 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ድረስ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- የባንክ አክሲዮን ሽያጭ ዝውውርን በተመለከተ የወጡ ህጎች እና መምሪያዎች ተፈጻሚ ይሆናሉ፡፡
- ጨረታው ጥር 07 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9፡30 ሰአት በዋናው መስሪያ ቤት 4ተኛ ፎቅ ካፍቴሪያ ውስጥ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ባንኩ ንብረቶቹን/አክሲዮኖቹን በገዢው ስም ለማዘዋወር ለሚመለከታቸው መንግስታዊ አካላት ደብዳቤ ይጽፋል፡፡
- ተጨማሪ እሴት ታክስ እና ሌሎች ገዥ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰኑ ክፍያዎችን ገዥ (የጨረታው አሸናፊ) ይከፍላል፡፡
- ባንኩ በማንኛውም ጊዜ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ለበለጠ ማብራሪያ ሕብረት ባንክ ዋና መስሪያ ቤት በስልክ ቁጥር 011 562 10 24 ወይም 0114 16 97 57 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!